Posted by The Ethiopia Observatory (TEO)

Credit: KalitiPress
ዛሬ ማለዳ ላይ አንድ የደሴ ወጣት ፍነው ለመውሰድ የሞከሩ ግለሰቦች በከተማው ወጣቶች ርብርብ ሊተርፍ እንደቻለ የአይን እማኞች ገልጸዋል።
ወጣቱ በአንድ የግል መኪና ውስጥ ታስሮ በጠመንጃ ታጅቦ ከከተማው በስውር ሊያስወጡት ሲሉ እንደተደረሰባቸው ነው የተነገረው።
አፋኞቹ በገመድ አስረው በጠመንጃ አጅበው የግል ታርጋ ባለው መኪና ይዘው በመውጣት ላይ ሳሉ ሁኔታውን የተጠራጠሩ የደሴ ወጣቶች ጀሜ በሚባለው ቦታ መኪናዋን በማስቆም ታሳሪዉን አስለቅቀውታል።
መኪናዋ ውስጥ የነበሩ አፋኞች እግሬ አውጭኝ ብለው ጠፍተዋል። መኪናዋ በደሴ ወጣቶች ቁጥጥር ስር ውላለች። ጋዜጠኞች ይምጡልንና ይህንን ግፍ ይዘግቡልን ማለታቸውን አንድ የአይን እማኝ በስፍራው ሆኖ ተናግሯል።
=================================================================================================================
==================================================================================================================
በርቱ ወጣቶች!
LikeLike