በከፍያለው ገብረመድኅን Posted by The Ethiopia Observatory (TEO)
ኢትዮጵያ ውስጥ ዝናብ ይጥፋ፣ የሚበላ ምግብና የሚጠጣ ጠፍቶ፥ ድርቅ የሕዝብ ቁጥር እንኳ ቢቀንስ፡፣ ቻይና የምትሰጠውን ብድር አፍንጫ ሰንጋ በወቅቱ ለማስከፈል ስምምነት ታስገባለች፤ ማስከፈል እንደምትችልም አበክራ ታውቃለች።
በተመሳሳይ መንገድ፥ ሩስያም በደርግ ጊዜ ሃገሪቱ ለጦር መሣሪያ የተበደረችውንና በ1998 አምስት ቢሊዮን ዶላር የነበረውን ዕዳዋን ‘በክፍያና በዕዳ ቅነሳ’ አሁን ወደ $126 ሚልዮን ወርዷልና፣ ‘ዘላለም በዚህ ልንቀጥል አንችልም’ በማለት ሞስኮ ሰሞኑን፡ ኢትዮጵያ ቻይናን ከምትቀልባት ፕሮጀክቶች ለእነርሱም ኩባንያዎች ድርሻ እንዲሰጣትና ዕዳውም እንዲከፈል በማለት ግልጽ ጥይቄ ማቅረቧን ስፑትኒክ የተሰኝው የሩስያ ሚድያ አስምቷል።
Continue reading