በከፍያለው ገብረመድኅን – The Ethiopia Observatory (TEO)
– ክፍል አንድ –
በዚህች በአሁኗ ሰዓት፣ በተለይ በኦሮሚያ የሕዝብ ተቃውሞ ጋብ ብሏል በሚባልበት ሁኔታ እንኳ፣ የሕወሃት አስተዳደር በግፍና ምሥጢራዊ መንገድ ሰዎችን – በተለይ ኦሮሞችን – በማጥፋት ላይ ነው። እንዲሁም፥ አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ ከአራት ያላነሱ የኦሮሞ ፌዴራል ኮንግሬስ አባላትና ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ከአዲስ አበባና ከዚያ ውጭም ያሉ አክቲቪስቶች ከፈረንጆች ገና ዋዜማ ጀምሮ በመታሠር ላይ እንደሚገኙ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲናና አቶ በቀለ ነገዓ ለኢሣት ታህሳስ 24 አረጋግጠዋል።
Continue reading